በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺህ ገደማ ተማሪዎች መካከል፤ ወደ ዩኒቨርስቲ መግቢያ የማለፊያ ነጥብ ያመጡት ተፈታኞች ብዛት 27,267 ተማሪዎች አሊያም 3.2 በመቶዎቹ ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 16,451 የማታ ተማሪዎች መካከል፤ ከ50 በመቶ በላይ ውጤት ያመጡት 12ቱ ብቻ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
እነዚህን አሃዞች ዛሬ ሰኞ መስከረም 28፤ 2016 በሰጡት መግለጫ ይፋ ያደረጉት፤ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ናቸው። ፕሮፌሰር ብርሃኑ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ባለፈው ዓመት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር “በጣም ከፍተኛ የሚባል መሰረታዊ ለውጥ የለም” ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ካስፈተኑ 3,106 ትምህርት ቤቶች መካከል፤ 1,328ቱ አሊያም 42.8 በመቶ የሚሆኑት አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ በዛሬው በሰጡት መግለጫቸው ይፋ አድርገዋል።
አምስት ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ ማሳለፋቸውንም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። ሌሎች አምስት ትምህርት ቤቶች ደግሞ ለፈተና ካስቀመጧቸው ተማሪዎች ውስጥ 94.5 በመቶ በላይ የሚሆኑትን ማሳለፋቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።
-----------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ [ Ссылка ]
ፌስቡክ ፦ [ Ссылка ]
ትዊተር (ኤክስ) ፦ [ Ссылка ]
ቴሌግራም፦ [ Ссылка ]
ቲክቶክ፦ [ Ссылка ]
Ещё видео!