+ ዛሬ⁉️ (ሹመት አምቢ ሲል)_ በግድ አስረው ጳጳስ አደረጉት! አባ መቃርስ ?
← ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም
A
..ill 100%
4▾
AA
#new #ማርያም #ተክለሃይማኖት #mezmur #abagebrekidan #መዝሙር #ሀብተማርያም #mikael #መዝሙረ_ዳዊት
መጽሐፈ ስንክሳር
ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም ፬
አባ መቃርስ ሊቀ ዻዻሳት
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ
ስም መስከረም አራት በዚች ቀን ቅዱስ አባት
የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ መቃርስ አረፈ ።
እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ከቍጥራቸው ውስጥ
ነው ።
ይህም አባት ከታናሽነቱ ጀምሮ በገድል የተጠመደ ሆነ
የምንኲስናንም ልብስ ሊለብስ ወዶ ወደ አስቄጥስ
ገዳም ወጣ ። በዚያም በመጀመሪያው አባት በአባ
መቃርስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መነኰሰ በምንኲስና
ያለውንም ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ ።
እርሱም ሁልጊዜ መጻሕፍትን የሚያነብና
ትርጓሜያቸውንም የሚያስረዳ ሁኗልና በትሩፋት ስራ
ከፍ ከፍ ባለ ጊዜ ቅስና ተሾመ ። ከእርሱ በፊት የነበረ
ሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤልም በአረፈ ጊዜ ኤጲስቆጶሳቱ
ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔዱ ።
ከእርሳቸውም ጋር ሃይማኖታቸው የቀና ብዙዎች
አዋቂዎች ካህናት ነበሩ በአስቄጥስ ገዳም ከሚኖሩ
ከታላላቅ መነኰሳትም ጋራ ስብሰባ አድርገው ለዚች
ለከበረች ሹመት ስለሚገባው ሰው እየመረመሩ ብዙ
ቀኖች ተቀመጡ ።
ከዚህም በኋላ የተሻለና ለዚች ለከበረች ሹመት የሚገባ
ይህን አባ መቃርስን አግኝተው ሊቀ ጵጵስና ሊሾሙት
ሁሉም በአንድ ምክር ተስማው ። ስለ ትሩፋቱና ስለ
ተጋድሎው በአስቄጥስ ገዳም የሚኖሩ ብዙ መነኰሳት
ምስክሮች ሁነዋልና ይዘውትም ሊሔዱ ያለ ፍቃዱ
ይዘው አሰሩት እርሱ ግን እንዲህ እያለ ይጮህ ነበር ።
እኔ ለዚች ለከበረች ሹመት የማልገባ ነኝ እናቴ ሁለት
ባሎችን አግብታ ስለነበር ይህንንም ያለው እንዲተዉት
እንጂ እናቱ ግን በአንድ ባል ብቻ የኖረች ሌላ
የማታውቅ ንጽሕት እንደሆነች ስለርሷ ብዙዎች
ምስክሮች ሁነዋልና ። ስለዚህ እሊቀ የተናገረውን
ምክንያት አልተቀበሉትም ።
ከዚህም በኋላ ወደ እስክንድርያ ወስደው ሊቀ ጵጵስና
ሾሙት ከዚያም ወደ ምስር አውጥተው በመዓልቃ
በሚገኘው አምላክን በወለደች በእመቤታችን በቅድስት
ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሹመቱ
ደብዳቤ በዮናኒ በቅብጥ በአረብ ቋንቋ ተነበበች ።
ከዚህም በኋላ በሹመቱ ወራት በጎ ስራ ትሩፋትን
ተጋድሎውን አብዝቶ የሚሰራ ሆነ ። ሁል ጊዜም
ለህዝቡ እግዚአብሔርን እንዲፈሩ ያስተምራቸዋል ስለ
ነፍሳቸውም ድኀነት ይገሥጻቸው ነበር ።
በሹመቱ ወራትም ከራሱ ከሚገባው ከግብሩ ለቤተ
ክርስቲያን ይሰጣል ለድኆችና ለችግረኞችም
ይመጸውታል እንጂ ከቤተ ክርስቲያን ገንዘብ ምንም
ምን አልወሰደም ። በሹመቱም ሃያ ሰባት ዓመት ኖረ
እግዚአብሔርንም አገልግሎ ደስ አሰኝቶ በሰላም
በፍቅር ሳለ አረፈ ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት
ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን ።
አርኬ
ሰላም ለመቃርስ በእስክንድርያ ዘተአምነ፡፡ መርዔተ
ክርስቶስ ይርዓይ መሲሐውያነ፡፡ ለእለ ኀረይዎ ሕዝብ
ዘይሰመዩ ኂራነ፡፡ ጸሊኦ ሲመተ እንዘ ውእቱ ኢኮነ፡፡
ወልደ ዳግሚት ብእሲት ይቤሎሙ አነ፡፡
በዚችም ቀን ለነዊ ልጅ ለኢያሱ መታሰቢያው ነው
ደግሞ በአንጾኪያ በሰማዕትነት የሞቱ የሁለት መቶ
ሰዎች መታሰቢያቸው ነው ። በረከታቸውም ከእኛ ጋር
ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።
መስከረም ፬ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.ቅዱስ ኢያሱ ወልደ ነዌ (ነቢይና መስፍን)
፪.ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ (ልደቱ)
፫.ቅዱሳን ዘብዴዎስና ማርያም ባውፍልያ
፬.አባ መቃርስ ሊቀ ዻዻሳት
፭.አባ ሙሴ ዻዻስ
ወርኀዊ በዓላት
፩.ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
፪.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
፫.ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ (ሰማዕት)
አሁንም እግዚአብሔርን ፍሩ ። በእውነተኛም ልብ
አምልኩት
.
•
ቢታያችሁ
•
•
•
እግዚአብሔርን ማምለክ ክፉ መስሎ
የአሞራውያንን አማልክት ታመልኩ
እንደ ሆነ: የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ ። እኔና ቤቴ
ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን ። (ኢያሱ ፳፬፥ ፲፬)
ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ እምእለ
ተፀመድኩ ዘልፈ ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ
መጽሐፈ እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውክፈ
እምእለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ ።
ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን ሰማዕታት
ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት
ኄራን ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን እስከ አረጋዊ
ልሂቅ እምንኡስ ሕፃን ።
ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ ዘአንበቦ
ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ
መንፈስ በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ ። ጌታ ሆይ
ከብልፅግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ
የደሀዪቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ
የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ
ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል ።
እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት
ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል
እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ
የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ ።
ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ
የጻፈውና ያጻፈውም ከግዕዝ ወደ አማርኛ
የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና
በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር
የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ
በአንድነት ይማረን ።
Ещё видео!