በመፈንቅለ መንግስት ወደ ስልጣን የመጡት የቡርኪናፋሶ፣ኒጀርና ማሊ ወታደራዊ ሁንታዎች በኮንፌደረሽን ለመዋሃድ ተስማሙ። ከምዕራብ አፍሪቃ የኢኮኖሚ ማሕበረሰብ ጥምረት ፍቺ መፈጸማቸውንም ገልጿል።
ግብጽ እስራኤል፣ ሐማስና አሜሪካ የሚሳተፉበት የሰላም ውይይት እንደምታዘጋጅ አስታውቃለች። የአሜሪካው ማዕከላዊ የደሕንነት መስሪያ ቤት ሹም ዊልያም በርነስ በዚሁ ጉዳይ ለመወያየት ወደ ኳታር ያመራሉ ተብሏል።
እስራኤል ዛሬ በጋዛ ባካሄደችው የአየር ጥቃት የፍልስጤም ግዛት የሰራተኛ ጉዳዮች ምክትል ሚኒስትር መገደላቸውን የጋዛ ባለስልጣናት አስታወቁ። ከባለስልጣኑ ጋር የነበሩ 3 ማንነታቸው ያልተገለጹ ሰዎችም መሞታቸውን ታውቋል።
የሮማው ርእሰ ሊቃነጳጳሳት ፍራንሲስ በዓለማችን ዴሞክራሲ ታሟል አሉ። ሊቀ ጳጳሱ ረዥም የተባለለትን የ16 ቀናት የእስያ ጉብኝታቸውን ከመጀመራቸው በፊት በጣልያን ትሪስቴ በተባለች ከተማ በአንድ የካቶሊክ ቤተክርስትያን በነበረው ሐይማኖታዊ ሥነስርአት ተገኝተው እንዳሉት በአውሮጳ ጽንፈኝነት እየተስፋፋ ነው።
ሩስያ በዩክሬይን ዶኔትስክ ግዛት የምትገኝ አንድ ተጨማሪ መንደር መያዟን አስታወቀች። ይህችው የድንበር ከተማ ቀጣይ ለምታካሂደው ወታደራዊ ዘመቻ ቁልፍ ቦታ መሆንዋንም አክላለች። በሌላ ዜና የዩክሬይ ድሮኖች ወደ ሩስያ ድንበር በመዝለቅ በአንድ ከፍተኛ ወታደራዊ መጋዝን ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን ታውቋል።
![](https://i.ytimg.com/vi/kxkVo919cZk/mqdefault.jpg)