ላለፋችሁት እንኳን ደስ አላችሁ!! ይሔንን ውጤት ለማምጣት ላልተሳካላችሁ በምንም አይነት ተስፋ የምትቆርጡበት አይደለም!!
ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
የኢዜማ መሪ እና የትምህርት ሚነስትር ሚኒስቴር
__________
በጣም ሊያስደነግጥ የሚችል ውጤት እንደሆነ እናውቃለን። እውነት ለመናገር እኛም መጀመሪያ ስናየው እስከሚገባኝ ድረስ ብዙ ቤተሰቦችም የዘንድሮው ውጤት ከበፊቱ በጣም የተዳከመ እንደሆነ ገምተዋል::
ብዙ ቤተሰቦች ይህን የፈተና አሰጣጥ ስንጀምር ልጆቻቸው ሊወድቁ እንኳን እንደሚችሉ እያወቁ የለም በንፅህና ቢያልፉ ይሻለናል ብለው ይህንን የፈተና አካሄድ ደግፈዋል።
ይህን ውጤት ሲያዩ በአጠቃላይ በአገር ደረጃ ይህች ሀገር ከነበረችበት የትምህርት ሥርዓት ወደተሻለና ልጆቹን ወደሚያበቃ፤ ነገ በዚህ ፈጦ በመጣብን የዓለም ውድድር ስርዓት ውስጥ ተወዳድረው ማለፍ የሚችሉ ልጆች የምናፈራበት ስርዓት መፍጠር ግዴታችን እንደሆነ ያውቃሉ ብለን እናምናለን።
በዚህ ምክንያት ነው ይሄ ተስፋ የሚያስቆርጥ አይደለም ይሄ የማንቂያ ደውል ነው፤ ተኝተን ነበረ ተጋግረን ነበር፤ አሁን ነቅተናል!! ከነቃንና በጋራ አብረን ከሰራን ይሔንን በጥቂት ዓመታት ውስጥ መቀየር እንችላለን ብዬ አምናለሁ።
ላለፋችሁት እንኳን ደስ አላችሁ!! ይሔንን ውጤት ለማምጣት ላልተሳካላችሁ በምንም አይነት ተስፋ የምትቆርጡበት አይደለም።
ከአሁን በኋላ ማወቅ ያለባችሁ ግን ሳየሰሩ፣ ሳይደክሙ፣ ሳያጠኑ እና ሳያነቡ ዕውቀት የለም፤ ትምህርት የለም። ያንን ይዛችሁ እስከሄዳችሁ ድረስ ለሚቀጥለውም ዓመት እድል አላችሁ።
Ещё видео!